Post by Ethio-CERT
2,050 followers
በጉግል አፕሺት (Google AppSheet) አማካኝነት 30,000 የፌስቡክ አካውንቶች ተጠለፉ። ******************** ከቪዬትናም ጋር ግንኙነት አለው የተባለ አዲስ የሳይበር ጥቃት ስምሪት፣ የጉግል አፕሺትን (Google AppSheet) እንደ "የማጥመጃ ማስተላለፊያ" (phishing relay) በመጠቀም የፌስቡክ አካውንቶችን ለመጥለፍ የሚያስችሉ የሐሰት መልዕክቶችን ሲያሰራጭ ተስተውሏል። ይህ እንቅስቃሴ በጋርዲዮ (Guardio) የደህንነት ተቋም "AccountDumpling" የሚል መጠሪያ የተሰጠው ሲሆን፣ የተሰረቁ አካውንቶች በጥቂቶቹ አማካኝነት በሚመራ ሕገ-ወጥ የገበያ ድረ-ገጽ ላይ መልሰው ይሸጣሉ። በጥቃቱ በአጠቃላይ 30,000 የሚሆኑ የፌስቡክ አካውንቶች እንደተጠለፉ ይገመታል። ተጨማሪውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://lnkd.in/dmtfA8sH የሳይበር ደህንነትን ለማጠናከር እና ወቅታዊ የመከላከያ መረጃዎችን ለማግኘት የ Ethio- CERTን ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ይከታተሉ። ተጨማሪ የሳይበር ደህንነት መረጃዎችን ለማግኘት፡- • ድረ ገጽ፦ https://lnkd.in/e_ZNJkew •ሊንክዲን (LinkedIn) ፦ https://lnkd.in/dWhnui6U •ቲክቶክ (Tiktok) ፦ https://lnkd.in/dYDfNbEY • የሳይበር ጥቃት ጥቆማ ለመስጠት ነጻ የስልክ መስመር፡ 933